Go to full page →

ኢየሱስ ሀዘናችንን እና ሥቃያችንን ያውቃል Amh2SM 237

ቀኑ ሰኔ 26 ቀን 1892 ዓ.ም ነበር፡፡ ሌሊቶች ረዥምና አስጨናቂ ስለነበሩ ሲነጋ ደስ ይለኛል፡፡ እንቅልፍ እምቢ ሲለኝ አንድ በፍጹም የማያንቀላፋ እየጠበቀኝ እንደሆነ ሳስብ ልቤ በምስጋና ይሞላል፡፡ እኛ የምንሸከመውን ስቃይና ሀዘን ሁሉ ኢየሱስ ማወቁ እንዴት አስደናቂ ነገር ነው፡፡ እኛ የሚደርስብን ሥቃይ ሁሉ እርሱም ደርሶበታል፡፡ ከጓደኞቻችን መካከል አንዳንዶቹ ስለ ሰብዓዊ መከራ ወይም አካላዊ ሕመም ምንም አያውቁም፡፡ ታመው ስለማያውቁ ታመው ያሉ ሰዎች የሚሰማቸው ስሜት ሙሉ በሙሉ አይሰማቸውም፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ የእኛ የድካም ስሜት ነክቶታል፡፡ እርሱ ታላቁ የህክምና ሚስዮናዊ ነው፡፡ እርሱ ፍርድንና ምህረትን ለማስታረቅ ሲል ሰብዓዊነትን በራሱ ላይ በመቀበል ራሱን የአዲስ ሥርዓት መሪ አድርጎ አስቀምጧል፡፡ -- Manuscript 19, 1892. Amh2SM 237.3