Go to full page →

ከሁሉ የተሻሉ አጽናኞች Amh2SM 274

ከባድ ሀዘን የደረሰባቸው ሰዎች ወደ ሄዱበት ሁሉ የፀሐይን ብርሃን በማምጣት ከሁሉ የተሻሉ አጽናኞች ናቸው፡፡ እንደ እነዚህ ያሉት የመከራን ተግሳጽ የተቀበሉና ሌሎችን ማጽናናት የሚችሉ ናቸው፤ መከራ በደረሰባቸው ጊዜ በእግዚአብሔር ላይ የነበራቸውን መታመን ሳይጥሉ ከመከራ ወደሚጠብቃቸው ፍቅር በመቅረብ የሙጥኝ ያሉ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ጨለማንና ብርሐንን ለሚፈጥር፣ እና ለጥቅማችን ለሚገስጸን፣ በገርነት ለተሞላው የእግዚአብሔር ጥንቃቄ ሕያው ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ክርስቶስ የዓለም ብርሐን ነው፤ በእርሱ ጨለማ የለም፡፡ ውድ ብርሃን! በዚያ ብርሃን እንኑር! ሀዘንን እና ተስፋ መቁረጥን ደህና ሰንብት በሉት፡፡ ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜም እላለሁ ደስ ይበላችሁ፡፡ -- Health Reformer, vol. 12, No. 10, October, 1877. Amh2SM 274.2