Go to full page →

ለጄ ኤም ጋርማየር የተላከ መልእክት Amh2SM 73

ወጥመድ ውስጥ እንድትገባ ለማድረግ ሰይጣን ነገሮችን አቀናጅቷል፡፡ ወግ አጥባቂነት፣ ማታለያ እና ጠንካራ ማሳሳቻ ይማርክሃል፡፡ ለጥቅሶች የተሳሳተ ትርጉም በመስጠት፣ የእግዚአብሔርን ቃል ከእውነተኛው ትርጉሙ በመለየት ሀሳቦችህን በቤተሰብህ ውስጥ ተናግረሃል፣ ከዚህ የተነሳ ሕዝባችን የያዛቸውና የሚያምንባቸው ነገሮች ትክክል አለመሆናቸውን እንዲያምኑ መርተሃቸዋል፡፡ አንተ ለመጽሐፍ ቅዱስ የምትሰጣቸው ትርጉሞች የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች ከያዙት አቋም ጋር የሚጣጣም አይደለም፡፡... {2SM 73.4} Amh2SM 73.4

ለልጆችህ አእምሮ የሰጠሃቸው ቅርጽ የራስህን አእምሮ ያበላሹ ስህተቶችን ይሸታል፡፡ በሌሎች ላይ ጉድፎችንና ነቁጣዎችን እንዲየዩና እንዲነቅፉ አስተምረሃቸዋል፡፡ በወንድሞች ላይ ክፉ በመናገርና ስህተታቸውን በመለቃቀም በቃልህና በምሳሌነትህ ሁኔታዎችን እንድንቀሳቀሱ አድርገሃል፣ ያውም የራስህ ኃይል ከሰይጣን ወኪሎች ጋር በመጣመር የሴት ልጆችህን ራዕዮች አስከትሏል፡፡ ይህ ስህተት መፈለግ፣ ወንድሞችን መክሰስ ሁሉ ሰይጣናዊ ነው፡፡... {2SM 73.5} Amh2SM 73.5