Go to full page →

በኃጢአትን ካባ ትእዛዛቱን መጠበቅ ChSAmh 59

በእግዚአብሔር ሕግ ጠባቂዎች መሃል _ ዛሬም ተመሳሳይ አደጋ ተጋርጦአል፡፡ የትእዛዛቱ ጠባቂዎች መሆናቸው ከመለኮታዊው ፍርድ ኃይል ሊታደጋቸው እንደሚችል አድርገው ራሳቸውን ይሸነግላሉ፡፡ አንዳንዶች ለሥራው እጅግ ቀናተኛ መስለው የእግዚአብሔርን አገልጋዮች ከመክሰስ በቀር ስለ hፉ ተግባራቸው ግሳጼ ለመቀበልና ለመታረም ፈቃደኞች አይደሉም፡፡ ኃጢአት የሚጠላው አምላክ ሕጉን የሚጠብቁ ወገኖች ከማናቸውም እርክስና እንዲርቁ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ ቃሉን እየታዘዙ ንስሐን ችላ ማለት በጥንታውያኑ እስራኤላውያን ላይ ተመሳሳይ ኃጢአት እንዳስከተለ ዛሬም በእግዚአብሔር ሕዝቦች ላይ የከፋ መዘዝ ይኖረዋል፡፡ ፍርዱን የማያዘገይበት የራሱ ልክ እና ገደብ አለው፡፡ Testimonies, vol. 4, pp. 166, 167. ChSAmh 59.1