Go to full page →

በውጭ የሥራ ቦታ የመሪዎች ያመራር ዘዴ GWAmh 313

አዲስ የሥራ ቦታ ሲቆረቆር ትምህርታዊ መሥሪያ ቤት ተቋቁሞ ቀስበቀስ ትምሀርት ሊሰጥ ይገባዋል፡፡ ዋና ተፈላጊነት ያለው ስብከት አይደለም፡፡ ቤት ለቤት እየዞሩ ቃሉን ማብራራትና ማስረዳት የበለጠ ተፈላጊነት አለው፡፡ GWAmh 313.2

ክርስቶስ ያስተማረበትን ዘዴ የሚከተሉ ሰዎች ነፍሳትን ለመሯሥለስ ይችላሉ፡፡ በመደጋገም አንድን ትምህርት ከማስተማሩም በላይ ሠራተኛው ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር ላይ ይተማመን፡፡ በጨለማ ያሉትን ሲያስተምር ጠቃሚ የመምህርነት ልምድ ያገኛል፡፡ ራሱም መማርን ስለማያቋርጥ በሚያስተምርበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በውስጡ ገብቶ ሰተራቡ ነፍሳት የሕይወትን አንጀራ እንዴት እአንደሚቆርስ ያስተምረዋል፡፡ GWAmh 314.1

በውጭ አገር የሚሠራ ስው ልዩ ልዩ ደረጃና አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ስለሚያጋጥሙት ልዩ ልዩ ያቀራረብ ዘዴዎች መጠቀም ይኖርበታል፡፡ የራሱን ደካማነት ከተገነዘበ ብርሃን፤ ብርታትና ዕውቀት ለመቀበል ወደ እግዚአብሔርና ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ይጠጋል፡፡ GWAmh 314.2

ያቀራረብ በዴያችንና ምክንያታችን ሁል ጊዜ አንድ ጦሆን የሰለበተም፡፡ ሚሲዮናዊ ማሰብና ማመዛዘን ይገባዋል፡፡ ከሥራ ልምድ የተነሳ በልዩ ልዩ አጋጣሚ በጣም የተሳካውን ዘዴ ሊገነዘብ ይችላል፡፡ በአንድ አገር ያልተለመዱ የሕዝበ ልምድና የአየር ጠባይ በሌላው ሲያጋጥሙ አሠራሩ ሁሉ ይለዋወጣል፡፡ በተቻለ መጠን ለውጥ ቢያስፈልግም ከመንገድ ላለመውጣት መጠንቀቅ : GWAmh 314.3

በጥቃቅን ነገሮች ላይ ጭቅጭቅ አንዳይነሳ መጠንቀቅ ነው። ሰዎች ልባቸውን ከምድራዊ ጣጣ መልሰው ወደ ሰማያዊ ነገር ቢመሩ የፍቅር መንፈስና የክርስቶስ ፀጋ እርስ በርሳቸው ያስተሳስራቸዋል፡፡ በዕውነት ኃይል ችግሮች ሊቃለሉ፤፣ ዘመናት የቆዩ አለመግባባቶች ሊወገዱ ይችላሉ፡፡ «ሰላም በምድር ላይ በጎም ነገር በሰው ፈቃድ» የሚለው ታላቅ መመሪያ ከሥራ ላይ ሊውል የሚችል በክርስቶስ ያመኑ ሁሉ ለእግዚአብሔር ሥራ ተባባሪ ሰ'ሆኑ ነው፡፡ GWAmh 314.4