Go to full page →

የተለያዩ ተሰጦዎች GWAmh 322

እግዚአብሔር አንድ ሰው ብቻውን የሚሠራበት የሥራ ቦታ ለማንም አይመድብም፡፡ አንዲያውም ይህ የአቅዱ ተቃዋሚ ነው፡ ሥራው በተዝረጋበት መስመር ሁሉ የተለያየ አስተሳስብና ተሰጦ ያላቸው ሰዎች በሕብረት እንዲሠሩ : ማንም ሰው ብቻውን ታላቅ ሥራ መሥራት ስሰማይችል አችላለሁ ብሎ ራሱን የሚያታልል እንዳይና'ር፡፡ አንድ ሰው አንድ የተለየ ችሎታ ካለው በሌሎች ነገሮች ሁሉ እንደአዋቂ ተገምቶ የሌሎች እርዳታ አያስፈልገውም እንዳይባል፡፡ GWAmh 322.2

በአንድ ላይ የሚሠሩ ሰዎች የግድ መግባባት የለባቸውም፡፡ ነገር ግን የማስተውለውን ከማያስተውሉ ጋር፣ እኔ የማሰበውን ከማያስቡ ጋር በሕብረት አልሰራም ማለት ትልቅ ሥህተት ነው፡፡ ሁሉም ትሁትና ለመታረም ፈቃደኛ የሆነ መንፈስ ቢኖራቸው ችግር የለም፡፡ ክርስቶስ ሰቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ሥጦታ አድሏታል፡፡ እነዚህ ስጦታዎች በያሉበት የተክበሩ ስለሆኩ በሕብረት ከተሠራባቸው ለክርስቶስ ዳግም ምፃት የተዘጋጀ ሕዝብ ሊያዘጋጁ ይትላሉ፡፡ GWAmh 322.3

በኋላፊነት ላይ ያሉ ወንጌላዊያኖችን እግዚአብሔር መርጧቸዋል፡፡ ከዚያ በፊት የነበራቸው ይዞታ ቦታ የለውም፡፡ ገበሬዎች አናዒዎች ወይም የኮሌጅ ምሩቃን ቢሆኑ እግዚአብሔር ከተቀበሳቸው ማንም ሰው አንዳይነቅፋቸው ይጠንቀቅ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ግምት ይሰጠው ይሆናልና ማንንም ሰው ዝቅ አድርገህ አትመልከት፣ በሰው ዘንድ ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው ሰዎች ስለልባቸጡ ክፋት በእግዚአብሔር ዘንድ ታናሾች ናቸው፡፡ GWAmh 322.4

የግል አስተሳሰባችንና ስሜታትን ተከታይ አንዲሆነኑ ሰዎችን በማግባባት ከጊዜያችን ንዑስ ክፍል ማባክን ክልክል ነው፡፡ ሰዎችን የሥራው ተባባሪዎች እንዲሆኑ፣ ተስማሚ ጠባይ እንዲኖራቸጡ የሚያሠለጥናቸው እግዚአብሔር ራሱ ነው፡፡ GWAmh 323.1

ሰዎች የተለያየ ዝንባሌና ተሰጦ ስላላቸው የአንድን ሥራ ቅርንጫዓ፡ አንዱ ከሌላው አብልጦ ሊያስተውለው ይችላል፡፡ አንዱ ሰው ሰመፈጸም ያቃተውን ወንጌላዊው በወንድሙ ይፈጽመው ይሆናል፡፡ አንድ ሰው ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በቂ ችሎታ አለኝ ብሎ ቢመካ ያ ሰው የእግዚአብሔርን ጸጋ አያገኝም፡: መለኮታዊ ተቀባይነት ያለው በታማኝነትና በሃይማኖት የሚካሄድ የፍቅር አገልግሎት ብቻ ነው፡፡ ወደ አግዚአብሔር የሚያቀርብ በመንፈስ የሚመራ እያንዳንዱ ሥራ በስማይ መጽሐፍ ተመዝግቧል፣ ሠራተኞቹም ይመሰገነብታል፡፡ በእነርሱ አማካይነት የዳነትን ሲመሰከቱ በንታ ደስ ይላቸዋል፡፡ በምድር በነበረው በእግዚአብሔር ሥራ በቂ ልምድ ስላላቸው ለሰማይ ሥራ ገጣሚዎች ይሆናሉ፡፡ አሁን የምናሳየው መልካም ጠባይና የምንፈጽመው መልካም ሥራ በሰማይ ለምንሆነው ምሣለሌ ነው፡፡ GWAmh 323.2