Go to full page →

የእግዚአብሔር ቃል በተሳሰሳቱ ሀሳቦች መበከል የለበትም Amh2SM 24

«እነሆ ክርስቶስ እዚህ ነው! እነሆ ክርስቶስ እዚያ ነው!” በሚል ግራ በሚያጋባ ጩኸት መካከል የተለየ ምስክርነት፣ ለዚህ ሰዓት ገጣሚ የሆነ የተለየ የእውነት መልእክት ይተላለፋል፡፡ መልእክቱ ተቀባይነት ሊያገኝ፣ ሊታመን እና ሥራ ላይ ሊውል የሚገባ መልእክት ነው፡፡ ጠቃሚው ነገር የተሳሳቱ ሀሳቦች ሳይሆኑ እውነት ነው፡፡ የቃሉ ዘላለማዊ እውነት በአሳሳች ሁኔታ ከተሳሉ አሳሳች ስዕሎች፣ ከሁሉም አታላይ ከሆኑ ስህተቶችና ሙታንን ከመጥራት ነጻ ሆኖ ይቆማል፡፡ በእግዚአብሔር ሕዝብ ሀሳብ ላይ ውሸት ተቀባይነት እንዲያገኝ በግድ ይገፋል፣ ነገር ግን እውነት በራሱ ውብና ንጹህ ልብሶች መሸፈን አለባት፡፡ ቃሉ፣ ቅዱስና ከፍ ከፍ ከሚያደርግ ተጽዕኖው የተነሳ ውድ የሆነ ስለሆነ፣ ወደ ተራና የተለመዱ ነገሮች ደረጃ ዝቅ ማለት የለበትም፡፡ ሰይጣን ቢቻለው የተመረጡትን እንኳን ሊያስታቸው በሚያመጣቸው የተሳሳቱ ሀሳቦች ሰይበከል ሁልጊዜ መኖር አለበት፡፡--The Review and Herald, Oct. 13, 1904. {2SM 24.1} Amh2SM 24.1

ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች እምነታቸው ምስቅልቅሉ በወጣበት የግርግር ቦታ ላይ ሳይሆን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የተመሰረተ፣ አዋቂ እና የሚያስብ ሕዝብ መሆናቸውን ዓለም እንዲመለከት የእግዚአብሔር ሕዝብ መስራት አለባቸው፡፡ ሰዎች የሕይወትን እንጀራ ተርበዋል፡፡ ድንጋይ አትስጡአቸው፡፡ --Manuscript 101, 1901. {2SM 24.2} Amh2SM 24.2