Go to full page →

አካላዊ መግለጫዎች አይፈለጉም Amh2SM 26

እውነተኛ ኃይማኖት ብዙ አካላዊ ማሳያዎችን (መግለጫዎችን) አይፈልግም፡፡ እነዚህ ነገሮች የእግዚአብሔር መንፈስ መገኘት ማስረጃዎች አይደሉም፡፡ በ1843 እና በ1844 ዓ.ም ላይ ይህን የመሰለ ወግ አጥባቂነትን ለመጋፈጥ ተጠርተን ነበር፡፡ ሰዎች መንፈስ ቅዱስ አለን እያሉ ወደ ስብሰባ ቦታ ይመጡና ልክ እንደ ቦንዳ ይንከባለላሉ፤ አንዳንዶች ይህን ድርጊት እንደ የእግዚአብሔር መንፈስ ሥራ ማስረጃ አድርገው ስላልተቀበሉ እንደ ክፉ ሰዎች ታይተዋል፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ዓይነት ጽንፈኝነት መካከል ላከኝ…፡፡ አንዳንዶች ይመጡና ለምን እነዚህን አትቀላቀያአቸውም ብለው ይጠይቁኝ ነበር፡፡ እኔም መልሼ እንዲህ አልኳቸሁ፡- ከዚህ ሌላ መሪ አለኝ፣ የእኔ መሪ በልቡ ትሁትና የዋህ የሆነ፣ እናንተ በዚህ ቦታ የምታሳዩአቸውን ዓይነት መግለጫዎች የማያሳይ፣ እነዚህን የመሳሰሉ የጉራ ተግባራት የማይፈጽም ነው፡፡ እነዚህ የሚታዩ መግለጫዎች የክርስቶስ ሳይሆኑ የሰይጣን ናቸው፡፡ --Manuscript 97, 1909. {2SM 26.3} Amh2SM 26.3