Go to full page →

ደካማ መንፈሳዊ vይወት ላይ መገኘት ChSAmh 52

የካበተ ብርሃን በእግዚአብሔር ሕዝቦች ላይ ቢያበራም ብዙዎች ይህን ብርሃን ለመከተል ችላ ብለዋል፡፡ በዚህም በታላቅ መንፈሳዊ ድካም ላይ ይገኛሉ፡፡ ዛሬ የእግዚአብሔር ሕዝቦች እየጠፉ ያሉት በዕውቀት ማነስ አይደለም፡፡ የሚኮነኑት-መንገድ፣ እውነትና ሕይወትን ባለማወቃቸው አይደለም፡፡ እውነትን ቢያስተውሉም፣ ሰማያዊው ብርሃን በነፍሳቸው ላይ ቢፈነጥቅም ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ችላ ተብለዋል ወይም ተቃውሞ ገጥሞአቸዋል፡፡ ሊቃወሙት የሚችሉት ብርሃን ያልበራላቸው ወገኖች በኩነኔ ስር አይወድቁም፡፡ ለእግዚአብሔር የወይን ተክል ከዚህ በላይ ምን መደረግ ይችላል? _ የከበረው ብርሃን _ በእግዚአብሔር ሕዝቦች ላይ ከማብራት ውጪ ሊድኑበት ፈቃዳቸው ካልሆነ፣ በበራላቸው ብርሃን መጠን በሙላት _ ካልተመላለሱና በጨለማ ላሉት ካላስተላለፉ በቀር ሊያድናቸው አይችልም፡:--Testimonies, vol. 2, p. 123. ChSAmh 52.1