Go to full page →

የመንፈስ ቅዱስ መምህርነት GWAmh 184

ሰዎች ፈቃደኞች ከሆነ እግዚአብሔር አንዳሉ ተቀብሉ ለአገልግሉቱ ያሰለጥናቸዋል፡፡ ሰው የእግዚአብሔርን መንፈስ ከተቀበለ ሰውነቱ ይጎለምሳል፡፡ በሙሉ የእግዚአብሔርን ሰው አእምሮ በተፈላጊው መንገድ ይዳብራል፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እግዚአብሔር የሚፈልግበትን ግዳጀ አስተውሎ ይፈጽማል፡፡ ደካማና ወላዋዩ ብርቱና ጽኙ ይሆናል፡፡ የማያቋርጥ ታዛዥነት የክርስቲያነ ጠባይ እስኪመስል ድረስ ክርስቶስንና ደቀመዝሙሩን ያቀራርባቸዋል፡፡ ግልጽና ሰፋ ያለ አስተሳሰብ ይኖረዋል፡፡ አመዛዛኝነቱ ጠለቅ ያለ፤ ናርዱ የተደላደለ ይሆናል፡፡ በጽድቅ ፀሐይ ሕይወት ሰጭነተ ኃይል አድጎ ተገቢውን ፍሬ ያፈራል፡፡ ክርስቶስ መንፈስ ቅዱስ ኃጢዓትን ድል ለማድረግ ከሚታገሉ ሰዎች ላይ እንዲያርፍ ተናግራል፡፡ GWAmh 184.3

የሰውን ኃይል በመለኮት ኃይል በማልበስ ድልን ያቀዳጀዋል፤ የተሰወረውን ይገልጽላቸዋል፡፡ መድኃኒታችን ለዋለልን ውለታ ታማኞች ሆነን ለመቆም እንዲያስችለን መንፈስ ቅዱስ የዕለት ጉልበታችን እንዲሆን ባይሰጠን ኖሮ ክርስቶስ ሰእኛ ሲል መፈተትዮ፤ መቸገሩ፤ መሞቱ፣ መነሣቱ ምን ይጠቅመን ነበር? መንፈስ ቅዱስ ደቀመዛሙርቱን እግዚአብሔርን እንዲያወድሱና አእንዲያሞግሱ እንዲያከብሩም አእረዳቸው፡፡ የቅዱሳንን ደራሲያን ብአእሮችም የክርስቶስን ሥራና ንግግር መዝግበው ለዓለም አንዲያበረክቱ መራቸው፡፡ ዛሬም GWAmh 184.4

የሰዎችን አስተሳሰብ ወደቀራኒዮ መስቀል ለመመለስ፣ ለዓለም የእግዚአብሔርን ለመግለጥ፤ ለዐመዐፀኛው ነፍስ የመጽሐና፡ ቅዱስን ተስፋዎች ለማስተዋወቅ መንፈስ ቅዱስ ያለማቋረጥ ይሰራል፡፡ GWAmh 185.1

የጽድቅን ፀሐይ ሙራ በጨለማው ስአምር ውስጥ የሚያበራ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የሰዎችን ልብ በዘለዓሰማዊ እውነት የሚያቃጥልም እርሱ ነው፡፡ ሰውን ኃጢዓቱን የሚያስገነዝበና የፅድቅን ከፍተኛ ክብር የሚያስታውቅ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የሰዎችን ልምድ ከሚያጠፉ ነገሮች ና:ቅር አሳቅቐ የዘለዓለም ሀብት አንዲወርሱ የሚረዳቸውም መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ GWAmh 185.2

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የሰማያዊ ቤተሰብ አባል ይሆኑት ዘንድ ያድሳቸዋል፤ ይቀድሳቸዋል፤ ይገራቸዋል፡፡ GWAmh 185.3