Go to full page →

ጉባዔውን አንዳይቀነስ ማድረግ GWAmh 265

አንድ ጊዜ ስብሰባ ከመደረጉ በፊት ሰዎች ለዝግጀት በሚመካከሩበት የምክክር ስብሰባ ተገኝቼ ነበር፡፡ የእኛ ማህበር በደንብ ስላልታወቀ ለማስታወቂያ የሚውል በርክት ያለ ገንዘብ ለመመደብ ይወያዩ ነበር፡፡ GWAmh 265.3

ከመካከላቸው አንዱ ብልህ እንዲህ አለ፡፡ «መጀመሪያ ድንካ'ናችሁን ትከሉ፤ ከዚያ በቷላ ማሳታወቂያ ብትናገሩ ብዙ ሥራ ይሠራል፡፡ መልፅክቱ በወረቀት ከሚታተም ይልቅ ሰውየው በሕይወት ቆሞ የሜስጠው ትምህርት የበሰጠ ተሰሚነት አለው፡ ግን ሁለቱም ዘዴዎች ሲተባበሩ የበለጠ ውጤት ያስገኛሉ፡፡ በየዓመቱ አንድ ዓይነት ዘዴ መከተል መልካም አይደለም፡፡ የፕሮግራሙን ዋደም ተከተል ቀያይሩት፡፡ ሰይጣን ዕድል ካገኘ ሥራውን ሁሉ አበላሽቶ ነፍሳትን ለማጥፋት ሥራ አይፈታም፡፡ GWAmh 265.4

«ሕዝቡ ነገሩን ሰምተው የሚነቅፉትንና የሚደግፉትን ለይተው ሳያውቁ ተቃውሞ አታነሳሱ። ገንዘባችሁ ከስብሰባው በ፲3ላ የበለጠ አገልግሎት አንዲሰጥ ከስብሰባው በፊት አታባክኑት፡፡ በስብሰባው ጊዜ ጽሑፎች እየተራቡ ቢዳረሱ ውጤቱ ያምራል፡፡» ይህ ምክር የተገለጠልኝ ከሰማይ ዘንድ ነው። ብልሁ መካሪ ያልሁትም ክርስቶስ ነው፡፡ GWAmh 266.1

በአንዳንድ ስብሰባዎቻችን ብዙ በቡድን በቡድን ሆነው ጽሑፍ በማደል ሰዎችን ሲያድሙ አይቻለሁ፡፡ በቢህ ምክንያት ሲቀሩ ይችሉ የነበር ሰዎች በስብስባው የመጨረሻ አጋማሽ በታማኝነት ሲመጡ ተመልክቻለሁ፡፡ ለሰዎች ብርሃንን ለማብራት ማንኛውንም ገዝክክለኛ መንገድ መሞከር አለብን፡፡ ዕውነቱን ለመከተል የሚፈል? አንዳንድ ሰዎት ከውጭ ተቃውሞ ሲገጥማቸው የሚመልሱት ይጠፋቸዋል፡፡ በስብሰባው የተነገረው ትምህርት በአጭሩ ተጠናቅሮ ለሕዝብ ይታደል፡፡ የንግግሩ ዋና ክፍል በጋዜጣ ታትሞ ቢወዐጣ መልካም ነው፡፡ ለተወሰኑ ሰዎች የተነገረው ዕውነት ለብዙዎች ለዳረስ ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ ተቃውሞ ቢሰሙ ሰዎቹ የሚመልሱት መልስ አያጡም፡፡ GWAmh 266.2