Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents
የክርስቲያን አገልግሎት - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ከመጀመሪያ አንስቶ በሥራ ላይ የሚገኘው መንፈስ ቅዱስ

    እግዚአብሔር ለወደቀው ዘር ያለውን ዓላማ ለማሳካት ከመጀመሪያ አንስቶ ሰብዓዊ ወኪሎቹን ተጠቅሞ በመንፈስ ቅዱስ ይሠራ ነበር፡፡ ይህ ሁናቴ በኃይማኖት አባቶች vይወት ተገልጾአል፡፡ በሙሴ ዘመን “ያስተምራቸው ዘንድ ቸር መንፈስህን ሰጠሃቸው” ተብሎ የተነገረ ሲሆን በሐዋርያት ዘመን ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ለቤተ ክርስቲያን እጹብ ድንቅ ነገሮች ተሠርተው ነበር፡፡ ለካሌብና ለኢያሱ እምነትና ወኔ የሰጠ፣ የኃይማኖት አባቶችን ደግፎ ያቆየና የሐዋርያትን ቤተ hርስቲያን ውጤታማ ያደረገ ያው ኃይል—በእያንዳንዱ ቀጣይ ትውልድ የእግዚአብሔርን ታማኝ ልጆች ደግፎ ይይዛል፡፡ በጨለማው ዘመን ይኖሩ ለነበሩት ዋልዴንስ ክርስቲያኖች የተሐድሶ ጎዳና የተቀየሰላቸው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ነበር፡፡ ዘመናዊውን የወንጌል ተልዕኮ ለማቋቋም ፋና ወጊ የነበሩትን ታዋቂ ወንዶችና ሴቶች ጥረትም ሆነ የመጽሐፍ ቅዱስን በልዩ ልዩ ቋንቋዎችና ዘዬዎች ትርጓሜ ውጤታማ ያደረገ—ያው መንፈስ ቅዱስ ነው: ፡— The Acts of the Apostles, p. 53. ChSAmh 355.1

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents