Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents
የክርስቲያን አገልግሎት - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ከፍ ያለውን አhሊል ማለም

    ደካሞች ወይም ፈሪዎች ልንሆን አይገባም፡፡ አብሮን የሚኖረውን አምላካዊ ክብር በምድራዊ ምቾት፣ ተድላ፣ ደስታ ወይም ለሥጋ ፍላጎት ማርኪያ መሸቀጥ ውጤቱ እጅግ አስከፊ ይሆናል፡፡ ከእግዚአብሔር እጅ የሚቸረው ስጦታ አሸናፊውን ይጠባበቃል፡፡ ይህ ለአንዳችንም የማይገባን ስጦታ--ያለ ምንም ክፍያ ከእርሱ በነፃ የሚሰጥ ነው፡፡ ስጦታው እጅግ ድንቅና የከበረ ቢሆንም “አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ በክብር እንደሚለይ” ማስታወስ ይኖርብናል፡፡ ከፍ ላለው ችሎታና ዕውቀት ብርቱ ጥረት እንድናደርግ እየተበረታታን በየሱስ ኃይል ወደ ምንቀዳጀው አክሊል እናነጣጥር፡፡ “ጥበበኞች እንደ ሰማይ ጸዳል፤ ብዙዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ”፡፡ Review and Herald, Oct. 25, 1881. ChSAmh 150.1

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents