Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents
የተመረጡ መልእክቶች (ሁለተኛው መጽሐፍ) - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    በድርጅቱ ውስጥ ለሚሰሩ ሰራተኞች የሚከፈል ደሞዝ

    የህትመት ሥራ የተመሰረተው በመስዋዕትነት ነው፤ የተጠበቀውም ልዩ በሆነ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፡፡ የጀመርነው በታላቅ ድህነት ነበር፡፡ ለመብላትም ሆነ ለመልበስ የሚበቃ ነገር አልነበረንም፡፡ የድንች እጥረት ከመኖሩ የተነሳ ዋጋቸው ከፍተኛ በሆነባቸው ጊዜያቶች በእነርሱ ፋንታ ታርኒፕ የሚባል ሥራ ሥርን እንመገብ ነበር፡፡ በሥራ ላይ በነበርንበት የመጀመሪያ ዓመት የሳምንት ገቢያችን ስድስት ዶላር ብቻ ነበር፡፡ ትልቅ ቤተሰብ ነበረን፤ ነገር ግን ወጪዎቻችንን ከገቢያችን እንዳይበልጥ አደረግን፡፡ የፈለግነውን ሁሉ መግዛት አልቻልንም፤ ፍላጎቶቻችንን መገደብ ነበረብን፡፡ ነገር ግን ዓለም የወቅቱን እውነት ብርሃን እንዲያገኝ ለማድረግ ወስነን ስለነበር መንፈስ፣ ነፍስና አካል ከሥራው ጋር ተጠላልፈው ነበር፡፡ ያለ እረፍት፣ ያለ አንዳች የደሞዝ ማበረታቻ አስቀድመን ወደ ሥራ በመግባትና አርፍደን በመውጣት ሰራን፡፡… እግዚአብሔርም ከእኛ ጋር ነበር፡፡ የሕትመት ሥራን ብልጽግና ሲከተለው መሆን እንደሚገባው የደሞዝ ጭማሪ ተደረገ፡፡ Amh2SM 191.2

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents