Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents
የወንጌል አገልጋዮች - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    አእምሮን ማዳበር

    አስተሳሰባዥን ማስፋት በጣም ነገር ነው፡፡ ያለንበት ጊዜ ጥልቅ አስተሳሰብ ዝቅተኝነት አና የአካባቢ አለመመቸት ለአእምሮ አድገት አንቅፋት ሊሆን አይችሉም፡፡GWAmh 180.2

    በማንኛጡም የትምህርት ጊዜ ችግር መኖሩ ባይካድም ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም፡፡ ተመራመሩ፤ አጥኑ፤ ጸልዩ። ችግርን በቀራጥነትና በወንድነት ተጋፈጡት፡፡ ፈቃደኝነትና ትዕግሥትን ጋሻችሁ አድርትጉ፡፡ ከዚያ በኋላ ተመስጣችሁ እውነት በግልጥ አምራና አጊጣ (ሀሳባችሁ)ካስተዋላችቸሏት በኋላ ለሌሎች አስተላልፉት፡ ግን ሥራ ሳትፈቱ የማያቋርጥ ምርምር አድርጉ፡፡ በዚህ መንገድ ምሥጢር በምስጢር ላይ ይጨምርላሳችንል (ይገልጥላች3ኋል)፡፡GWAmh 180.3

    በዚህ አቅጣጫ ሁለት ዓይነት ድል ተቀዳጃችሁ ማለት ነው፡፡ ጠቃሚ ትምህርት ከማትረፋትሁ በላይ አእምሮከችሁ ሥራን ተለማመደ ማለት አንድን ምስጢር የከፈተው ቁልፍ ሌሎችን ምስጢሮች የሚከፍቱትን ቁልፎች ያዘጋጃቸዋል፡፡GWAmh 180.4

    ብዙዎቹ ወንጌላዊያን ሊያስተምሩ የሚችሉት ላይ ላዩን ነው፡፡ ጥረታቸውን ቢያጠነክሩት ኖሮ ጠለቅ አድርገው ለመመራመር በቻሉ ነበር። ትንቢቶችና ሌሎችም መሠረተ- አምነቶችን ወንጌላዊያን ጠንቅቀው ማወቅ ይገባቸዋል፡፡ ጥቂቶች ወንጌላዊያን ባወቁት በትንሱ ተወስነው ይኖራሉ፡፡ ስንፍናቸውን ትተው በጸሎትና በትጋት ቅዱስን ቢመራመሩ እነርሱን የሚያህል የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቅ ባልተገኘም ነበር፡፡ የክርስቶስን ሕይወትም በግልጽ ባስተዋሉት ነበር፡፡GWAmh 180.5

    የማንኛውም ወንጌላዊ ጭንቅላት የዕውቀት ጎተራ መሆን አለበት፡፡ በተፈለገ ጊዜ ካከማቸው ዕውቀት ሳይቸገር አፍሶ መዝራት የሚኘል መሆን አለበት፡፡ ሰዎች ጠንቅቀው ባለመመራመራቸው አእምሮአክቸው ሊሳግትና ሊደንዝ እግዚአብሔር ወደ ፊት ሂዱና የሰጠጊችሁን ችሎታ ሥሩበት የሜልበት ጊዜ መጥቷል፡፡GWAmh 181.1

    ዓለም በስህተትና በተረት ተጥለቅልቋል፡፡ ውሰት በልብወለድ ስም ሆኖ የሰዎቭሻን የአእምሮ ችሎታ ጠቃሚ ነገር ከማሰብ አዘንግቶታል፡፡ የእግዚአብሔር ሰዎች የሚገጥማቸውን ተቃውሞ ለመቋቋም አጥብቀው የሚመራመሩ፤ አስተዋዮች፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀት የበሰሉ መሆን አለባቸው፡፡GWAmh 181.2

    በሃይማኖት መጋረጃ የተጋረደን ኩራት፤ ውሱንነተ አና ጥራዝ ነጠቀነት መቀበል የሰብንም፡፡ የአውነጉ ኃይል በልባቸው የሰፈነባቸው ሰዎች ተደማጭነት ይኖራቸዋል፡ ሐሰት እውነትን አንደማያሸንፍ አውቀው ረጋ ያሉና አደብ የገዙ ይሆናሉ፡፡GWAmh 181.3

    ከወንጌላዊያኖቻችን መካከል ምንም ሳይሠሩ ዝነኛ ለመሆን የሚሱ አሉ፡፡ የክርስቶስ አገለጋይ ለመሆን የሚያበቁአቸውን ጥቃቅን የፅለት ተግባሮች ሳያከናውኑ ከፍተኛ ሞያ ለመሥራት ይንጠራራሉ፡፡ ለሥራው ብዙ የሚያደርጋቸው ፳ነኑ መመሪያ ሳይኖራቸው የሌሎችን ሥራ ለመሥራት ይሞክራሉ፡፡ ይህ በወንዶችም በሴቶችም ያለ ከትሎታቸው በላይ ያለውን ሥራ የመሥራት ፍላጎት በተሰለፉበት ተግባር አንዳይሳካላቸው ምክንያት ይሆናል፡፡ ቀላል ዘዴ በመሻት በመሰላል አማካይነት ደረጃ በደረጃ ለመውጣት አሻፈረኝ ይላሉ፡፡GWAmh 181.4

    ያለፉት ሰዎች ምሣሌነት የሰውን ምንነትና የሰውን ተግባር ሲያስረዳን የጽድቅን ሥራ ለማካሄድ ማመጻችን የሚያስገርም ነው፡፡ ሁሉ ሰው ከፍተኛ ማዕረግ አይኖረውም ይሆናል፣ ግን ሁሉም በእየተመደበበብት የሥራ ክፍያ በታማኝነት ቁመው ከተገኙ ታማኝነታቸው ከገመቱት የበለጠ መልካም ውጤት ሊኖረው ይችላል፡፡GWAmh 181.5

    የሰዎች ተፈላጊነት የሚገመተው በሚሠሩት የሥራ ዓይነት አይደለም፡፡ ለእያንዳንዱ ነፍስ ዋጋውን የሚከፍለው ፈራጅ ይወስነዋል፡፡ በፍቅር፣ በትህትና፣ በሕብረት ክርስቶስን በልባቸው የተቀበሉ ሁሉና የክብራቸው ተስፋ ያደረጉት የክርስቶስ ሠራተኞች የመባል መብት አላቸው፡፡ የሰውና የአምላክ መገናኛው ፍቅር ስለሆነ የክርስቶስ ፍቅር በልባቸው ያለ ሰዎች ሕይወታቸው ይሰምራል፡፡ ክርስትና ማለት፤ ክርስቶስ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር በላይ ሰላምም በምድር ላይ የሰውም ፈቃድ፡፡ የእግዚአብሔርን ሃሳብ ማሟላት ማለት ይህ ነው፡፡ እውነተኛ የክርስትና አድገት የክርስቶስ ወደ መሆን ያደርሳል፡፡ እውነተኛ የአእምሮ ብስለት የሚገኘው ልብ በመንፈስ ቅዱስ ሳይነካ ሕግንና ደንብን ለመጠበቅ በመሞከር ሳይሆን በክርስቶስ ትምህርት ቤት በመማር ነው፡፡GWAmh 182.1

    የክርስቶስ ተከታይ በአስተሳሰብ፣ በልምድ፣ በመንፈስና በሥራ ሁልጊዜ መሳሳል አለበት፡፡ ይህን ማድረግ የሚቻል ማዶ ማዶ በመመልክት ሳይሆን ወደ ክርስቶስ አተኩሮ በማየት ነው፡፡ ይህ የሆነ እንደሆነ የአአእምሮ፣ የመንፈስና የጠባይ መለወጥ ይገኛል፡፡ ከክርስቶስ የተማረ ክርስቲያን ትሁትና ገር ይሆናል፡፡ ለሰማይ ቤተሰብነት ገጣሚ ይሆናል፡፡GWAmh 182.2

    አእምሮው በእግዚአብሔር ቃል የበራ ሰው ከማንኛውም ስሰው ይልቅ የክበደ ኃላፊነት ስለተጣለበት ምርምርና ጥናት ይወዳል፤ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት አዘውትሮ ይመረምራል፤ ተፈጥሮንም ያጠናል፡፡ ከዕውቀት ምንጭ ጋር ግንኙነት ያለው ሰው የመንፈስና የአእምሮ ዕድገቱ አይቋረጥም፡፡ እግዚአብሔርን ማወጠቅ ጥበብ ነው፡፡ ይህንም ተፈላጊ ዕውቀት ዕውነተኛ የሆነ ሠራተኛ ሁሉ በጥብቅ ይከታተለዋል፡፡GWAmh 182.3

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents