Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents
የወንጌል አገልጋዮች - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ዕድገትና አገልግሎት

    የክርስትና ኑሮ ብዙዎች ከሚያስቡት የተለየ ነው፡፡ በጨዋነት፣ በትፅግሥች፣፤፣ በደግነትና በገርነት ብቻ አይወሰንም፡፡ እነዚህ ጠባዮም ተፈላጊዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን ድፍረት፤ ኃይል፤ ብርታት፣፤ ትጋት ካልተጨመረበት ክርስትና አካለ ጎደሎ ነው፡፡ ክርስቶስ የተረከልን መንገድ ጠባብና ራስን መካድ የሚጠይቅ ነው፡፡ በዚህ መንገድ : ፈተናንና የሚቋፈቋቋመሙ- በመንፈስ ብርቱ ሰዎች ናቸው፡፡GWAmh 187.2

    አንቅፋትና መሰናክል ከመንገዳቸው ላይ ተሰቀሞ ለስላሳ ጎዳና የማይጠባበቁ፤ በንቃታቸው ሰነፎችን የሚያበረታቱ፤ በክርስትና ናቅር ልባቸው የሞቀ፣ የጌታቸውን ሥራ ለመፈጸም በአጭር የታጠቁ ብርቱ ሰዎች ያስፈልጋሉ፡፡GWAmh 187.3

    በሚሲዮናዊዌነት ሥራ የተሰለፉ አንዳንድ ሰዎች ደካሞች ፣መንፈስ የጎደላቸው፤ በቀላሉ የሚስነፉና ቶሎ ተስፋ የሚቆርጡ ናቸው፡፡ ድፍረት ይጎድላቸዋል። የትጋትና የሥራ ወዳድነት መንፈስ ይጎድላቸዋል፡፡ ለማሸነፍ የሚሰለፉ ሁሉ ደፋርና በተስፋ የተከበቡ መሆን አለባቸው፡፡ ዝም ለማለት ብቻ ሳይሆን ለመስራት መነሳሳት አለባቸው፡፡ ቁጣን ሰማብረድ ለስላሶት መሆን ሲገባቸው ክፉን ለመቋቋምም ጀደግኖች መሆን አለባቸው፡፡ ሁሉን በሚያስችለው ጸጋ ምሣሌነታቸው ትምህርታዊ እንዲሆን ሊጣጣሩ ይገባል፡፡GWAmh 188.1

    አንዳንዶች የሀሳብ ጽኑነት የላቸውም፡፡ በዕቅዳቸውና በአስተሳሰባቸው ዘላቂነትና ብቁነት የሳቸውም፡፡ ይህ ደካምነት፣ ወላዋይነትና ገ- ድለት መወገድ አለበት፡፡ በክርስትና ሕይወት ውስጥ በችግርና በመከራ እንኳን የማይናጋ ጠባይ መኖር አለበት፡፡ የማይስነገል፤ የማይታሰለልና የማይስፈራራ የሀሳብ ጽናት ሊኖረን ይገባል፡፡GWAmh 188.2

    ማንኛውንም አጋጣሚ ለሥራው ዝግድት አናውለው ዘንድ የእግዚአብሔር ምኛት ነው፡፡ ያለ ኃይላችን በሙሉ በሥራው ላይ እንድናውለው፤ ሀሳባችን በሙሉ የሥራውን ቅዱስነትና የኃላፊነቱን ከባድነት እንዲገነቨዘብ ይፈልግብናል፡፡GWAmh 188.3

    መልካም ሥራ ለመፈጸም ብዙ ሰዎች መከራቸው መጠነኛ ስለሚሆን የሥራቸው ውጤትም አጥጋቢ አይሆንም፡፡ በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ሰዎት በአኗኗራቸው ተግባር የሌላቸውና ዓላማ የሌላቸው መስለው ያልፋሉ፡፡ ከምክንያቶቹ አንዱ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው መገመታቸው ነው፡፡ ክርስቶስ ክቡር ዋጋ ስለከፈለበን ጠቃሚ ነር አንድንኖር ይፈልግብናል፡፡GWAmh 188.4

    ባሳችሁበት ዝቀተኛ ደረጃ መንፈሳችሁ በቃኝ አይበል፡፡ ልንሆን አንደምንችለውና እግዚአብሔር ልንሆን አእንደሚፈልኘሣብን አልሆንም፡፡ እግዚአብሔር የማመዛዘን ችሎታ የሰጠን እንድንከባክበውና እንድናጎለምሰው፣ ለስሰማያዊና ለከፍተኛ ለሚሜያደርሰን ሀሳብ እንድናውለው እንጂ እአንድናሳግተው ወይም ለምድራዊ ጥቃቅን ጥቅሞች አውለነው እንድናደኩረው አይደለም፡፡GWAmh 188.5

    በየትኛውም የሥራ ገበታ ብትሰለፉ አላማችሁ ጠባይን ማጎልመስ መሆነን አትርሱ፡፡ ምንም ዓይነት ሥራ ብትሠሩ በትጋትና በትክክለኛነት ሥሩት አንጂ ከዚያ የቀለለ ሥራ በመሳት አእምሮአችሁን አታስንፉት፡፡ በእየቀኑ ሥራችን የሚያድርብን ስሜት ሰዘመናችን ሁሉ መመሪያ ይሆነናል፡፡ ለተወሰነ ሥራ የተወሰነ አበል ለማግኘት ብቻ የሚሠሩ፣ ያለ ችግርና ያለ መ.ከራ ከደረጃ ወደ ደረጃ ለማለፍ የሚፈልጉ በእግዚአብሔር ሥራ ውስጥ ተፈላጊነት የላቸውም፡፡ የአካል የአአምርና የመንፈስ ጉልበታቸውን ቆጥበው የሚለግሙ ሰዎች ከእግዚአብሔር ዘንድ የተትረፈረፈ በረከት መቀበል አይችሱም። መጥፎ ምሣሌነታቸውም ተላሳፊ ነው። ዋናው መመሪያቸው «ለራሴ» የሚል ነው፡፡ ተቀጣጣሪ የማያስፈልጋቸውና የተወሰነ የሥራ ድርሳ አንዳላቸው የሚሰማቸው ለሥራው ገጣሚነት የላቸውም፡፡- የሚፈልጉት የሠራተኞች ዓይነት. ኃይላቸውን፣ ብርታታቸውን ፣፤ ተባባሪነታቸውንና ትጋታቸውን የማይቀጥቡ ናቸው፡፡ ለመስራት ፈቃደኞች የሆኑ ሠራተኛ ማለት እነርሱ ናቸው፡፡ ብዙዎች የማይሳካላቸው ያልሀ'ነልን እንደሆን በሚል ፍራቻ ከኃላፊነት በመገለላቸው (በመወገዳቸው) ነው፡፡ ስለዚህ ከንባብና ከትምህርት የማይገኘውን ታላቅ የሥራ ልምድ ያጣሉ፡፡GWAmh 189.1

    ሰውየው አጋጣሚዎችን መፍጠር አለበት አንጂ አጋጣሚዎች ሰውየውን ሊለውት አይገባም፡፡ አጋጣሚን ሥራ የምንሠራበት መሣሪያ አድርገን መገመት አለብን፡፡ ልናክው እንጂ ሊያዘን አይገባም፡፡GWAmh 189.2

    ብርታት የሚያገኙ ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ የተገፉ ተቃዋሚ የሚበዛባቸውና የተንገላቱ ናቸው፡፡ ያለ ጉልበታቸውን በሥራ ላይ በማዋል የተደቀነባቸውን መሰናክል ሁሉ ያልፉታል፡፡ በራሳቸው መተማመንን ይማራሉ፡፡ በችግርና በድንግርግር መክንያት በእግዚአብሔር ማመንና ጸንቶ መቆም ይማራሉ፡፡GWAmh 189.3

    ክርስቶስ የተወሰነ አገልግሎት አልሰጠም፡፡ የሥራ ጊዜው የተወሰነ ሰዓት አልነበረውም፡፡ ጊዜው፣ ልቡ፤ ሕይወቱና ብርታቱ በሙሉ ሰብዓዊ ፍጥረትን ለማገልገል የተመደበ ነበር፡፡ ቀን በሥራ ሲለፉ ውሎ የበለጠ ሥራ ለመሥራት ተጨማሪ ኃይል ሰመቀበል ሴሊት ደግሞ በጸሎት ጎብጦ ያድር ነበር፡፡ ሰብዓዌ ተፈጥሮው ብርታት ያገኝ ዘንድ፣ የጠላትን ብልፃተኛ ዘዴ ድል ለመንሳት እንዲችል፣ የሰብዓዊ ፍጥረትን ደረጃ ከፍ ለማድረግ የመጣበት ግዳጅ ይሳካለት ዘንድ ተማህጽኖውን ከልብ ያቀርብ ነበር፡፡ ሰሠራተኞቹ «አንደሠራሁት ትሠሩ ዘንድ ምሣሌ ሆችኞችኋለሁ» (ዮሐ. 13፡15) አላቸው፡፡GWAmh 189.4

    ጳውሎስ «የክርስቶስ ያስገድደናል» (2 ቆሮ. 5፡14) : ይህ የሕይወቱ መመሪያ ነበር፡፡ ዋና ዓላማውና ብርታቱም እርሱ ነበር፡፡ ከሥራ መስመሩ አንድ አፍታ ቢንሰራተት ወደመስቀሉ በመመልከት ትጥቁን ያጠብቅና ራሱን ክዶ ወደፊት ይጓዛል፡፡ ለወገኖቹ ለሚሰጠው አገልግሎት ብርታት የሚሰጠው የክርስቶስ ፍቅር መሆነን በና:ጹም ልቡ አምናበታል፡፡GWAmh 190.1

    የሚክተለው ተማህጽኖው እውነተኛና ልብን የሚነካ ነው፡፡ «የጌታችንን የየሱስ ክርስቶስ ቸር ሥጦታ አውቃች3ልፍ ሀብታም ሲሆን እናንተ በርሱ ባለጠግነት ሀብታም ትሆኑ ዘንድ ደዛ ሆነ፡› ከነበረው ከና:ተኛ ክብር ወደ ዝቅተኛ ደረጃ አንደ ታውቃላችሁ፡፡ መስዋዕትነቱን እስኪ ፈጽም ድረስ ምንም ከመንገዱ ፈቀቅ አላለም፡፡ በሰማያዊ ዙፋንና በመስቀሉ መካከል ማረፊያ አላገኘም።፡ ለሰምትች ስላለው ፍቅሩ ውርደትንና ስድብን በፈቃደኝነት ተቀበለ። ጳውሎስ የሚክተለውን ምክር ይስጠናል፡፡ «እአእያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት ለባልንደራው ደግሞ እንጂ ፤ በክርስቶስ የነበረ ይህ ሀሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ : እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት አንደሚገባ ነገር ስልቀጠረውም፡፡ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰው ምሣሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፡ በምስሉም እንደሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፡፡ ሰሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት ድረስ የታዘዘ ሆነ፡፡» (ፊል. 2፡4-8) ክርስየቶስን የግል መድኃኒቱ አድርጎ የሚቀበል ሁሉ እግዚአብሔርን ለማገልገል ይጓባጓል፡፡ የተደረገለትን ሰማያዊ ውለታ ሲያስብ ልቡ በፍቅርና በአገልግሎዮት ስሜት ይሞቃል፡፡ ምሥጋናውን ለመግለጽ ችሎታውን ለእግዚአብሔር ክብር ለማዋል ይነሳሳል፡፡ ፍቅሩን በደሙ ለገዛው ለክርስቶስ ይገልጣል፡፡ ሥራን፣፤ ፈተናን፣ መስዋዕትነትን አይፈራም፡፡ እውነተኛ የእግዚአብሔር ሠራተኛ እግዚአብሔርን ለማክበር የቻለውን ያህል ከመስራት አይቀጠብም፡፡ የእግዚአብሔርን ተትፅዛዝ በማክበር ሁልጊዜ የቀናውን ለመሥራት ይጣጣራል፡፡GWAmh 190.2

    ትሉሎሉታውን ለማሳሻል ጥረቱ አይቋረጥም። የሚሠራውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር ያደርጋል፡፡ ጠቅላላ ምኞቱ ክርስቶስን ማገልገልና ማክበር ነው፡፡ አንድ በቀንበርና በመሰዊያ መካከል በቀመ የበሬ ስዕል ላይ የተጻፈ «“ለሁሉም ዝግጁ ነው» የሚል ጽሑናፍ፡ ነበር፡፡ ይህም ማለት ቢጠምዱተም ይጠመዳል፤ ቢያርዱትም እንቢ አይል ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር እውነተኛ ልጅም በሰደዱት ሁሉ ቀጥ ብሎ ማገልገል አለበት፡፡ ራሱን ክዶ ለአዳኙ አገልግሉት መሥዋፅት መሆን አለበት፡፡ ራሱን ክዶ ለአዳኙ አገልግሎት መሥዋዕት መሆን አለበት፡፡GWAmh 191.1

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents