Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents
የወንጌል አገልጋዮች - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ቤተሰቦችን መጎብኘት

    ወንጌላዊ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያስተምረው ትምህርት የሥራው መጀመሪያ : ሲፈጽመው የሜገባው ብዙ የግል ሥራ አለው፡፡ ከሰዎች ጋር በግል ለመነጋገርና ለመጸለይ በየቤታቸው ሊጎበኛቸው : ወደ የቤታቸው አየሄደ ካሳስተማራቸው እውነቱ ሊደርሳቸው የማይችሉ ቤተሰቦች አሉ፡፡ ይህን የሚፈጽሙ ሰዎች ልባቸው በክርስቶስ ልብ ጋር መተባበር አለበት:: «ወደ መንገድ ወጥታችሁ አላፊ አግዳሚውን ሁሉ ጠርታችሁ ወደቤቴ አንዲገቡ አድርጓቸው: (ሉቃስ 14፡23) ወንጌላዊያን በየቤቱ እየዞሩ ያስተማሩ አንደሆን ሰዎችን በበለጠ ይቀርቧቸዋል፡፡ ከክርስቶስ ጋር ሲተባበሩ መንፈሳዊ ልብስ ያጎናጽፋቸዋል፡፡ በስሚዎቻቸው ልብ የሚገባውን ቃል ያቀብላቸዋል፡፡GWAmh 116.2

    እያንዳንዱ ወንጌላዊ «በክርስቶስ ወንጌል አላፍርም” ማለት አለበት፡፡ የሚጠቅማችሁን አንድ ሳላስቀር አስተማርሁአችሁ” : (ሐዋ. 20፡ 20፤21፤27)GWAmh 116.3

    መድኃኒታችን የታመሙትን ሲያክም፣፤ ያዘኑትን ሲያጽናና፣ ሰላምን ሲያበሥር ከቤት ወደቤት ይዞር ነበር:: ሕጻናትን አቅፎ በመባረክ ለተቸገሩት እናቶች የተስፋ ቃል ይናገራቸው ነበር፡፡GWAmh 116.4

    በርህራሄና በደግነት ማንኛውንም የሰው ችግር እየተቀበለ መፍትሄ ይሰጥ ይሰራ የነበር ለራሱ ሳይሆን ለሰዎች ነበር፡፡ ለሁሉ አገልጋይ : ምግብና መጠጡ የደከሙትን ማበርታት፣ ያዘኑትን ማስደሰት ከፈሪሳዊያን ወግና ሥርዓት የተለየውን እውነት ከእርሱ ሲሰሙ ሰዎች ልባቸው በተስፋ ::ትምህርቱ ከልብ ስለሆነ የሰዎችን ልብ የመመሰስ ኃይል ነበረው፡፡GWAmh 116.5

    ለወንጌላዊያን «በግል አገልግሎታችሁ ሰዎችን ካሉበት ችግር አውጧቸው› እላለሁ። ተዋወቋቸው፡፡ ይህ ሥራ ምትክ አያገኝም:: ገንዘብ መስጠት ወይም ማበደር አይደለም፡፡ በመድረክ ላይ የተስበከ ስብከት የግል አገልግሎትን ያህል ጠቃሚነት የለውም፡፡ ቤት ለቤት እየዞሩ ጥቅስን ማስጠናት ከቤተክርስቲያን ስብከት ጋር ሲተባበር ዋጋ አለው፡፡ ቤተሰብን የቤት ለቤት ገብኝትን ካልጨመረበት ስብከት ብቻ ዋጋ ላይኖረው ይችላል፡፡ እውነትን የሚሹ ሰዎችን በየጊዜው ማግኘት አለባቸው፡፡ አለበለዚያ ሰይጣን ያጠቃቸዋል፡፡ ነፍሳትን ስታስተምሩ እንቅፋት ቢገጥማችሁ አትደነቁ።: ሥራችሁ የጠበቃችሁትን ያህል ውጤት ባያሳያችሁ አትፍሩ፡፡ ሥራችሁን ቀጥሉ፤ የምትናገሩበትንና የማትናገሩበትን ጊዜ ለይታችሁ ዕወቁ፡፡ የሰዎችን ዝንባሌ በመመዘን ሰይጣን የሚቀርብበትን አቅጣጫና ዘዴ ካላወቃችሁ ትወድቃላችሁ፡፡ በችግር ምክንያት ዕምነታችሁ ላልቶ ጥረታችሁ አይቀነስ፡፡ በሃይማኖት መታጠቂያ ታጥቃችሁ ችግርን ድል ንሱት ::GWAmh 117.1

    ዘሩን በአምነትና በማይዝል እጅ ዝሩት፡፡ አቀራረባችሁ የሥራችሁን ውጤት ይወስነዋል፡፡ የሰላምታ አሰጣጣችሁና የአጅ አጨባዛበጣችሁ ሁኔታ ብቻ ሰውየው አንዲያምንባችሁ ወይም አንዲጠራጠራችሁ ሊያደርገው ይችላል፡፡GWAmh 117.2

    ግንኙነታችን እንደምስኪኖች አንደ ቆጠርናቸው ማሳት የለበትም፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ እነርሱም አንደ እኛ የተወደዱ ናቸው: የምንጎበኛቸው ሰዎች በኑሮ ደረጃቸው ዝቅ ያሉ ከሆኑ አለባበሳችን ቀለል ያለ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም የእነርሱን ኑሮ ከእኛ ጋር በማመዛዘን ቅሬታ ሊሰማቸው አይገባም፡፡ የነውር ችግር ያለባቸው ሰዎች በቀላሉ ቅሬታ ይሰማቸዋል፡፡ ታዲያ የእግዚአብሔር አገልጋይ ያላስደሰታቸውን ማን ያስደስታቸዋል፡፡ በየሱስ ያለ ደግነት ካሳላደረብን የሰዎችን ልብ ልናስደስት አንችልም፡፡GWAmh 117.3

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents